መንግስት ሀገራችን ከነበረችበት ድህነትና ኋላቀርነት ለማላቀቅ የህብረተሰቡን የኢኮኖሚና ማህበራዊ የላቀ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፎችን እየለየና በሂደት ዘርፉን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በመቅረጽና ወደ ተግባር በመግባት ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የበርካታ ዜጎችን የስራ አጥነት ችግር በመቅረፍ ኑሯቸው እንዲሻሻል እየተደረገ ይገኛል፡፡

የልደታ ክፍለ ከተማ አገራችን ኢትዮጵያ የበለጸገችና መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ በማሰለፍ የህዝቧን የኑሮ ሁኔታ ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማሻሻል የሚያስችል መዋቅራዊ አደረጃጀት በመፍጠር ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ሀገራዊ የድህነት ቅነሳ ግብን ለማሳካት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች ላይ ትገኛለች፡፡

የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የዘርፉን አዲስ የልማት ስትራቴጂ ማጽደቅ ተከትሎ በአዲስ መልክ ተደራጅቶ በስትራቴጂው የተቀመጡ ተልዕኮዎችን ለመወጣት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ጽ/ቤቱ በተዋቀረው በእያንዳንዱ የስራ ሂደት መደባዉን ሳይጠብቅ አሁን ባለዉ አደረጃጀት ሊተገበሩ የሚገባቸውን ተግባራት ከከተማው መሪ እቅድና ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመነሳት ዝርዝር እቅዶችን በማውጣት እየተገበረ ይገኛል፡፡

ጽ/ቤቱ ለተገልጋዮች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም ተገልጋዮች ወደ ጽ/ቤቱ አገልግሎት ለማግኘት ሲመጡ የሚሰጣቸውን የአገልግሎት ዓይነትና ጥራት፤ የሚወስደውን ጊዜ አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጋቸው ወጪና እንዲሁም በእነርሱ በኩል ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን ያመላከተ የተገልጋዮች ቻርተር ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡

የዜጎች ስምምነት ሰነድ ዓላማ

  1. ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የከተማዋን የህዝብ ቁጥር ታሳቢ በማድረግ ለቀጣይ ሁለት የስትራተጂክ ዘመናት ሊኖር የሚችለውን የህዝብ ቁጥር ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህንን ሊሸከም የሚችል የማህበራዊ ተቋማት ለመገንባት፤
  2. ግልፀኝነትና ተጠያቂነት ያለው የአሰራር ስርአት ለማስፈን፣
  3. አገልግሎት አሰጣጡ በተጠናው ስታንዳድ መሰረት እንዲሰጥ ለማድረግ፣
  4. በስታንዳርዱ መሰረት አገልግሎት የማይሰጡ አካላት ላይ ተጠያቂነትን በማስፈን የመልካም አስተዳደር ቸግሮችን መፍታት ናቸው፡፡
  5. ሁሉም ተገልጋዮች በስራ ኢንተርፕራይዝ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የባለቤትነት ስሜት ተሰምቷቸው አስተያየት ጥቆማና ማናቸውንም ግብዓት በነጻነት የሚሰጡበትን ሁኔታ ለማመቻቸትና ለመተግበር ነው፡፡

ስትራቴጂያዊ የትኩረት መስኮች (Starategic Themes)

  1. የሥራ ስምሪት በማስፋፋት የስራ ዕድል መፍጠር
  2. መሰረት የሚጥል ዘርፍ እንዲሆን ማስቻል፣
  3. በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚ ማድረግ
  4. የመስሪያ ቦታ ልማትና አቅርቦት
  5. ምቹ የሥራ ቦታና አካባቢ መፍጠር

የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት

    የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት በዝርዝር ለማወቅ ከፈለጉ ይህን Duties and Responsibility ይጫኑ

የተገልጋዮች መብት

  1. ምንም ልዩነት ሳይደረግበት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የመሆን፣
  2. ማንኛውም ተገልጋይ በአገልግሎቱ አሰጣጥና በአገልግሎት ሰጪው ቡድን/ሠራተኛ ላይ ያለውን አስተያየትና ቅሬታ የማቅረብ፣
  3. በጽ/ቤቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዝርዝር የማወቅና የመጠቀም፤
  4. ተገቢ የሆነ ድጋፍና እገዛ የማግኘት፤
  5. ቀልጣፋ አገልግሎት የማግኘት፤

የተገልጋዮች ግዴታዎች

  1. ሕጎችንና የአሰራር መመሪያዎችን መከተል
  2. ለሚፈልጉት አገልግሎት የተሟላና ትክክለኛ መረጃ የማቅረብ፣
  3. ተገልጋዬች አገልግሎት ለማግኘት ሲመጡ
    ተፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን የማሟላት