በልደታ ክ/ከተማ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎች ዜና
በልደታ ክ/ከተማ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎችን በፎቶ
በልደታ ክ/ከተማ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎች በቪዲዮ
በልደታ ክ/ከተማ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት መግለጫዎች
በክ/ከተማው ውስጥ የሚገኙትን ነዋሪዎች አምራች ዜጋ ለማድረግ የሚያስችሉ አዳዲስ የስራ ዕድል አማራጮችን ይለያል፣ ያጠናል፣ ያስጠናል፣ ፕሮጀክት ፕሮፋይል ያዘጋጃል፣ የአዋጭነት ጥናቶችን ያጠናል፣ ያስተዋውቃል፣ ወደ ስራ እንዲገቡ ያበረታታል፤
የኢንተርኘራይዞች የኢንደስትሪዎች የሥራ ፈላጊዎችንና የስራ ገበያ መረጃ ይመዘግባል፤ መረጃ ይሰበስባል፣ ይተነትናል፣ ያደራጃል፣ይተነትናል ጥቅም ላይ እንዲውል ያደርጋል፤
ለሥራ ፈላጊዎች ለኢንተርፕራይዞችና ኢንደስትሪዎች በሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ፣ አሰራርና የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ ግንዛቤ ይፈጥራል፤ አፈፃፀሙን እየተከታተለ ድጋፍ ያደርጋል፤
የኢንተርኘራይዞችና ኢንደስትሪዎች የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ያቋቁማል፣ ያስተባብራል፣ ይቆጣጠራል፤
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎችን በንግድ ህጉ እና አግባብ ባለው ሌላ ህግ መሰረት ያደራጃል፤ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል፤
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ በአግባቡ ማካሄድ የሚያስችላቸው የብድር፣ የካፒታል ሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፤ የመስሪያና መሸጫ ቦታ ይሰጣል፤ ተፈፃሚነቱን ይከታተላል፤ ያረጋግጣል፣ ከታለመለት ዓላማ ዉጭ ጥቅም ላይ ዉሎ ሲገኝ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ያስወስዳል፤
በኢንተርኘራይዝና ኢንደስትሪ ልማት ለተሰማሩ አንቀሳቃሾችና አምራቾች የሙያ ማበልፀጊያ ስልጠናዎች እና አውደ ርዕዮች እንዲዘጋጁ ያደርጋል፤
የኢንተርኘራይዞችና ኢንደስትሪዎችን የገበያ ችግር ለመቅረፍ ከተለያዩ አካላት ጋር የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ያደርጋል፤ ኤግዚቢሽንና ባዛሮች እንዲዘጋጁ ያደርጋል፤ በውጭ ሀገር በሚካሄዱ ኤግዚቢሽንና ባዛሮች እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፤
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች ለተወዳዳሪነታቸው እንቅፋት የሆኑ ጉዳዩችን በጥናት በመለየት መፍትሔ እንዲያገኙ ያደርጋል፤ ምርጥ ተሞክሮዎችን ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገር ለይቶ ያጠናል፣ ይቀምራል፣ ያስተገብራል፣ ውጤታማነቱን ይከታተላል፤
የኢንተርፕራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች እርስ በእርስ በግብዓት አቅርቦት፣ በምርትና በቴክኖሎጂ ትስስር እንዲፈጥሩ ያደርጋል፤ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር የገበያ ትስስር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፤
ኢንተርኘራይዞችና ኢንደስትሪዎች ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከጥናትና ምርምር ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ይሰራል፣
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች የመረጃ፣ የቴክኖሎጂ መረጣ፣ የድርድር፣ የግንባታ፣ የኮሚሺኒንግ ድጋፍ ይሰጣል፤ ውጤቱንም ይገመግማል፤
ለኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች የመረጃና የምክር አገልግሎት የሚሰጥበት የአሰራር ስርዓት ይዘረጋል፤ ተፈጻሚነቱን ይከታተላል፤
የኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች የብቃት ማረጋገጫ እንዲሁም የደረጃ እና የጥራት ሰርቲፊኬሽን እንዲያገኙ ድጋፍ ያደርጋል፤
ኢንተርኘራይዞችንና አምራች ኢንደስትሪዎች ከጥቃቅን ወደ አነስተኛ፤ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛና ከመካከለኛ ወደ ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ እንዲሸጋገሩ ያደርጋል፤
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች ተወዳዳሪ ለማድረግ በጥናት ላይ የተመሰረተ የማበረታቻ፣ የዕውቅና እና ሽልማት ስርዓት ይዘረጋል፤ ተግባራዊ ያደርጋል፤
የኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች በዘርፍ ማህበራት ያደራጃል፤ ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል፤
የኢንዱስትሪውን ምርትና ምርታማነት በቀጣይነት ሊያሣድጉ የሚችሉ የአቅም ግንባታ እና ችግር ፈቺ የጥናት ስራዎችን ያከናውናል፤ እንዲሁም የሰራተኞች የስራ ላይ ደህንነት፤ የአካባቢ ጥበቃና የኢንዱስትሪ ሰላም የሚያስጠብቁ ተግባራትን ያከናውናል፣፣
ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመቀናጀት ለኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች አስፈላጊ የሆነ የሰለጠነ የሰዉ ኃይል እና የግብዓት አቅርቦት አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማሟላት የሚያስችል ስልት ይቀይሳል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፣
ለኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች አገልግሎት እንዲውሉ የተዘጋጁ ነባር የመስሪያ ቦታ የሆኑ ህንጻዎች፣ ሼዶች፣ ተለጣፊ ሱቆች እና ኮንቴነሮች እንዲሁም በመንግስት፣ በግልና በተለያዩ በጎ አድራጎት ድርጅቶች የተገነቡ መደብሮችን ያስተዳድራል፤ ይከታተላል፤
ለኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች ማምረቻ፣ ማሳያ እና መሸጫ ሼድና ህንጻ በኢንደስትሪ መንደሮች፣ በክላስተር ማዕከላትና በገበያ ማዕከላት ማስገንባት እንዲችል ከሚመለከተው አካል የለማ መሬት ይረከባል፤ ካርታ የሌላቸው ነባር ይዞታዎች ካርታ እንዲሰራላቸው ያመቻቻል፤ የተገነቡትን ያስተላልፋል፤ ያስተዳድራል፤
ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች ማምረቻ፣ ማሳያ እና መሸጫ ሼድና ህንጻ በኢንደስትሪ መንደሮች፣ በክላስተር ማዕከላት፣ በገበያ ማዕከላት እና በኢንፖሪየም ማዕከላት በማደራጀት እንዲገነቡ ያደርጋል፤ እድሳትና ጥገና እንዲደረግላቸው ያደርጋል፤ የመሠረተ ልማት አውታሮችም እንዲሟሉላቸው ይደግፋል፤ ይከታተላል፤
ነባር እና አዲስ የመስሪያ ቦታ ማዕከላት ስታንዳርድ እና ዝርዝር የአፈጻጻም መመሪያ ያወጣል፣ ይተገብራል፣ ይቆጣጠራል፤ በወጣው መመሪያ መሰረት ለኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች በኪራይ ያስተላልፋል፤ ኪራይ እንዲሰበሰብ ያደርጋል፤
የመስሪያና መሸጫ ቦታዎች፣ ክላስተር ማዕከላትንና ኢንፖሪየሞችን በክላስተር ፅንሰ ሀሳብ መሰረት ዲዛይን እንዲዘጋጅ በማድረግ ማሰገንባት፣
መስራት እየቻሉ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት ሥራ ሳይኖራቸው በከፋ ድህነት ላይ የሚኖሩ የከተማ ነዋሪዎችን መረጃ ይመዘግባል፤ ይለያል፤ ያደራጃል፤ ይተነትናል፤ ሲፈቀድለትም በማህበረሰብ አቀፍ ልማት ስራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፤ አፈፃፀሙን ይከታተላል፤
ከማህበረሰብ አቀፍ ልማት ስራዎች የተጠቃሚነት ጊዜያቸው ሲያበቃ የማስመረቅ ስራ ይሰራል፤ በዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፤ አፈፃፀሙን ይከታተላል፤
በአሰሪና ሠራተኛ መካከል የሥራ ቦታ ሰላም እንዲሰፍን ያደርጋል፤ የወል የሥራ ክርክሮች እና የኅብረት ስምምነት ድርድር ልዩነቶች በመግባባት እልባት እንዲያገኙ ያደርጋል፤ የህብረት ስምምነቶችንና ማሻሻያቸውን ይመዘግባል፤
በአሰሪና ሠራተኛ መካከል የሥራ ቦታ ሰላም እንዲሰፍን የትምህርትና የሥልጠና አገልግሎት ይሰጣል፣ የሙያ ምክር አገልግሎት ስለሚስፋፋበት፣ ክፍት የሥራ መደቦች ስለሚመዘገቡበትና ሥራና ሠራተኛ ስለሚገናኙበት ዘዴ ይቀይሳል፤ ሲጸድቅም ተግባራዊ መሆኑን ያረጋግጣል፤
አሰሪዎች የስራ ሁኔታን፣ የሙያ ደህንነትና ጤንነትንና የስራ አካባቢን ለመጠበቅ የወጡ የስራ ሁኔታ ደረጃዎችና የመከላከያ ዘዴዎች በሥራ ላይ ማዋላቸውን ይቆጣጠራል፤
ሥራና ሠራተኛ ለሚያገናኙ ኤጀንሲዎች የብቃት ማረጋገጫ በህግ መሰረት ይሰጣል፤ ድጋፍ ያደርጋል፤ መሥራታቸውን ያረጋግጣል፤ ይሰርዛል፤
በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ህግ መሰረት የከተማው አስተዳደር የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ እና አማካሪ ቦርድ አባሎችን ይሾማል፤ ያሰናብታል፤ ተግባርና ኃላፊነታቸውን ይከታተላል፤
ሥራና ሠራተኛ ለሚያገናኙ ኤጀንሲዎች እና የግል የስራ ሁኔታ ቁጥጥር አገልግሎት አቅራቢዎች የብቃት ማረጋገጫ መስጠት፤
ለስራ ወደ ውጭ አገር ለመሄድ ፍላጎት ላላቸው ዜጎች ስለተቀባይ አገር ሁኔታ በሚሰማሩበት የስራ መስክ ሊኒራቸወው ስሚገባ ክህሎት፣ስለመብታቸውና ኃላፊነታቸው እና ስለመሳሰሉት ጉዳዩች የቅድመ-ስምሪትና የቅድመ ጉዞ ግንዛቤ ማሰደጊያ ስልጠና እንዲያገኙ ያደርጋል፣
ስለውጭ አገር ሥራ ስምሪት እና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥራዎችን መስራት፤
መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ እና ከግል ድርጅቶች ጋር ትስስር በመፍጠር ኢንተርኘራይዞችና አምራች ኢንደስትሪዎች ድጋፍ እንዲያገኙ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣ የአሰራር ስርዓት ይዘረጋል፣ተፈጻሚነቱን ያረጋግጣል፤
በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞችና አምራች ኢንዱስትሪዎች የአምራችነት ፍቃድ ይሰጣል፣ ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ በህጉ መሰረት ሳይሰራበት ሲቀር ፍቃዱን ይሰርዛል፣ በሰጣቸው የአምራችንት ፍቃድ መሰረት የማምረት አቅም ይለካል፣ የምርት ጥራት ቁጥጥርና ኢንስፔክሸን ስራዎችን ይሰራል፣ ከህግ ውጪ ተፈጽሞ ሲገኝ ህጋዊ የማስተካከያ እርምጃ ይመስዳል